lördag 23 oktober 2010

ጸድቅ አቡነ ሃብተ ማሪያም



ታላቁ ጸድቅ አቡነ ሃብተ ማሪያም ከተከበሩና ህገ እግዚአብሔር ጠብቀው በትሩፋት ከሚተጉ በንጽህናና በቅድስና ይኖሩ ከነበሩ አባታቸው ፍሬ ብሩክ ከ እናታቸው ዮስቴና ከተባሉ በመንዝ አዉራንጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ተወለዱ።

እናታቸው የምነና ሃሳብን ለመፈጸም ወደ አንድ ገዳም በሚሄዱበት ወቅት አንድ መነኩሴ "ምንኩስና ለአንቺ አልተፈቀደም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰዉ ሁሉ የሚማጸነው ስሙ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት በአፀደ ስጋ በአፀደ ነፍስ የሚያማልድ በምድር ሆኖ መንበረ ጸባኦትን የሚያይ ወንድ ልጅትወልጃለሽ " ባላቸው መሰረት የተወለዱና በእናታቸው ጀርባ ታዝለው ክህኑ በቤተክርስትያን "እግዚኦ ማሀረነ ክርስቶስ" ሲል በህፃን አንደበታቸው "እግዚኦ ማሀረነ ክርስቶስ"ይሉ ነበር ።

ባደጉ ጊዜ ትምህርታቸዉን ከጥሩ ስነ ምግባርና ህግን ከመጠበቅ ጋር ጠንቅቀው ከመማር ባሻገር በ አባ ሳሙሄል እጅ ምንኩስናን ተቀብለዋል።
ከአቡነ መልከ ፃዲቅ ገዳም ተነስተው ሲሄዱ መንገድ ላይ ከ አንድ ዋሻ ዉስጥ ለ ሶስት ወራት በ ጸሎት ቆይተዋል እግዚአብሔር "መታሰቢያህን በዚህ ዋሻ አደርገውዋለዉ" ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል ።
ይህ ዋሻ ዩሰበይ አባ ሃብተ ማሪያም ገዳም በመባል ይታወቃል . ከደብረ ሊባኖስ ዝቅ ብሎ በእግር 2ሰዓት መንገድ ላይ ያለዉ ን በሰበይ የተባለዉንም ገዳም በስማቸው መሰረቱት ፅንሰታቸው ነህሴ 26 ልደታቸው ግንቦት 26 ነ እረፍታቸው ኅዳር 26 ቀን ነው የፃድቁ አባታቺን የአቡነ ሃብተማሪያም ጸሎት እና አማላጅነት በሁላችን ላይ አድሮ ይኑር ።

Inga kommentarer:

Skicka en kommentar